አጫጭር የስፖርት ዜናዎች

38

ባሕር ዳር: ነሐሴ 14/2016 ዓ.ም (አሚኮ)👉 ራሂም ስተርሊንግ ጁቬንቱስን ሊቀላቀል እንደሚችል ተሰምቷል። እንደ ሜል መረጃ ስተርሊንግ በቼልሲ ቤት ቆይታው አልተረጋገጠም።

👉 ወልቭስ የአርሰናሉን ግብ ጠባቂ አሮን ራምስዴልን በውሰት ለማስፈረም እየሠራ ነው። በአትሌቲክ መረጃ መሰረት ወልቭስ ራምስዴልን በውሰት ማስፈረም እና በቀጣይ ዓመት ደግሞ በቋሚነት ማዛወር ነው የፈለገው።

👉 ፉልሃም ስኮት ማክቶሚኒን ከዩናይትድ ለማስፈረም ጥረት ላይ ነው። ቲም ቶክ እንዳስነበበው ፋልሃም ለማክቶሚኒ ዝውውር ለዩናይትድ ሁለት ጥያቄ አቅርቦ ውድቅ ተደርጎበታል።

👉 ኒውካስትል ማርክ ጉሂን ከፓላስ ለማስፈረም የሚያደርገውን ጥረት ቀጥሏል። በአማራጭነት የሊቨርፑሉን ጆ ጎሜዝን እና የቼልሲው ቻላባህ ለማግኘት እያሰበ ስለመኾኑ ያስነበበው አይ ስፖርት ነው።

👉 ቼልሲ ለሮሚዮ ሉካኩ ዝውውር 34 ሚሊዮን ፓውንድ ይፈልጋል፤ እንደ ቢቢሲ መረጃ ናፖሊ የሉካኩ ፈላጊ ሲኾን ቼልሲ ሉካኩን በቋሚነት እንጂ በውሰት ለመስጠት ፈቃደኛ አይደለም።

👉 ጋርዲያን ደግሞ ማንቸስተር ዩናይትድ ኡጋርቴን ለማግኘት እስከ ዝውውር መስኮቱ መጨረሻ ድረስ እንደሚሠራ ጽፏል። ድርድሩ ካልተሳካም በውሰት ተጫዋቹን ለማግኘት ማቀዱም ተሰምቷል።

👉 የሳኡዲው አል ሂላል ከማንቸስተር ሲቲ ካይል ዎከር እና ጃኦ ካንሴሎን የማስፈረም ፍላጎት እንዳለው የጋርዲያን መረጃ ያሳያል።

👉 ማንቸስተር ሲቲ ኢልካይ ጉንዱጋንን ከባርሴሎና መልሶ ለማስፈረም ፍላጎት አሳይቷል። በአትሌቲክ መረጃ መሰረት ጀርመናዊዉ ጉንዱጋን ከባርሴሎና እንዲወጣ የስፔኑ ክለብ ፍላጎት ነው።

👉 ሪያል ሶሴዳድ ማይክል ሚሪኖን ለማስፈረም አርሰናል ያቀረበውን ገንዘብ አልተቀበለም። ተጫዋቹ አርሰናልን ለመቀላቀል እንደሚፈልግ ሚረር አስነብቧል።

👉 ብሬንት ፎርድ አጥቂው ኢቫን ቶኒን ለሳኡዲው አል ሃሊ ለመሸጥ አቅዷል። ታይምስ እንደሚለው የእንግሊዙ ክለብ ከተጫዋቹ ዝውውር 50 ሚ ፓውንድ ይፈልጋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleጃኦ ፊሊክስ ቼልሲን ለመቀላቀል ተስማማ።
Next articleየአዲስ አበባ ከተማ የደን ሽፋን ከነበረበት 2 ነጥብ 8 በመቶ ወደ 17 በመቶ ማሳደግ መቻሉ ተገለጸ።