“በዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ አንድ እመርታ የታየበት ደረጃ ላይ ደርሰናል” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)

24

ባሕር ዳር: ነሐሴ 14/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮ ቴሌኮም ከቪዛ ኩባንያ ጋር በመተባበር በኢትዮዽያ የመጀመሪያውን በኪስ የሚያዝ ‘ቨርቱዋል ቪዛ’ ካርድ ብሎም የተሻሻለ የሀዋላ አገልግሎት በቪዛ ዳይሬክት እና በቴሌብር ረሚት አቅርቧል።

ይህንን አስመልክቶም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልእክት “በዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ አንድ እመርታ የታየበት ደረጃ ላይ ደርሰናል” ብለዋል።

ቪዛ ዳይሬክት ከ190 ሀገራት በላይ ቀለል ያለ የገንዘብ ማዘዋወር አገልግሎትን በቴሌብር ቨርቱዋል ካርድ ቁጥር አማካኝነት የሚያቀላጥፍ ይኾናል።

ይህ አዲስ አገልግሎት ከ47 ነጥብ 55 ሚሊዮን በላይ የኾኑ የቴሌብር ተጠቃሚዎችን ያገለግላል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮ ቴሌኮም ትልቅ ሥራ ሠርቷል ነው ያሉት።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article”ሥራ ማቆም የችግራችን መፍትሔ አይኾንም” የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች
Next articleበሕጻን ሄቨን ላይ ስለተፈፀመው ፀያፍ ወንጀል የምርመራ፣ ክስ እና ፍርድ ሂደት በተመለከተ ከአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የተሰጠ አጭር ማብራሪያ፡-