የድሬዳዋ አሥተዳደር የምክክር ተሳታፊዎች አጀንዳዎቻቸውን ለኮሚሽኑ አስረከቡ።

12

ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 11/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የድሬዳዋ ከተማ አሥተዳደር የምክክር ተሳታፊዎች አጀንዳዎቻቸውን ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዛሬ በይፋ አስረክበዋል።

በኮሚሽኑ አስተባባሪነት በድሬዳዋ አሥተዳደር ከነሐሴ 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረክ ዛሬ ተጠናቋል፡፡

የኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች አምባሳደር መሐሙድ ድሪር እና ኮሚሽነር ተገኘወርቅ ጌጡ (ዶ.ር) የድሬደዋ አሥተዳደር አጀንዳዎችን በይፋ መረከባቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article24 በርሚል ቤንዚን በሕገወጥ መንገድ ሲቀዳ መያዙን የወልድያ ከተማ አሥተዳደር አስታወቀ።
Next articleበአይሻ አንድ የነፋስ ኃይል ማመንጫ 300 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚያስችል ሥምምነት ተፈረመ።