የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመላው ኢትዮጵያ የሲስተም ማሻሻያ ሥራ እየተከናወነ መኾኑን ገለጸ።

53

ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 11/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመላው ኢትዮጵያ የሲስተም ማሻሻያ ሥራ እያከናወነ በመሆኑ በአንዳንድ የሀገሪቱ ክፍሎች ከፍተኛ የኃይል ጭነት በሚበዛባቸው ሰዓታት ዛሬና ነገ የኃይል መቋረጥ ሊያጋጥም እንደሚችል አሳውቋል።

የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ እንደገለጸው “ተቋሙ የማሻሻያ ሥራው አጠናቅቆ መደበኛ የኃይል አቅርቦት እስሰሚመለስ ድረስ፤ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉና ሌሎች ጊዜያዊ የኃይል አማራጮች እንድትጠቀሙ በአክብሮት እናሳውቃለን” ብሏል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በባሕር ዳር ከተማ ውስጥ የተፈጠረ የጸጥታ ችግር የለም” የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን
Next articleበአማራ ክልል ገበያን ለማረጋጋት ለፍጆታ የሚውሉ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለተጠቃሚው መቅረቡ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ፡፡