በሰቆጣ ከተማ የአረንጓዴ አሻራ እና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።

34

ሰቆጣ: ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ሰቆጣ ከተማ “የምትተክል ሀገር የሚያጸና ትውልድ” በሚል መሪ መልዕክት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።

በመርሐ ግብሩ ከአረንጓዴ አሻራ ጎን ለጎን የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ እና ለተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ እየተካሄደ ነው።

የፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር የበጎ ፈቃድ ተግባራትን እያከናወነ ሲኾን በዚህም ከ3 ሺህ በላይ ችግኞች በትምህርት ተቋማት አካባቢዎች ተተክለዋል።

በመርሐ ግብሩም የፕላን እና ልማት ሚኒስቴር፣ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን፣ የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ሥራ አሥፈጻሚዎች፣ የሰቆጣ ከተማ አሥተዳደር መሪዎች፣ የሰቆጣ ከተማ ነዋሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የሰቆጣ ከተማ ወጣቶች እየተሳተፉ ነው።

ዘጋቢ፦ ደጀን ታምሩ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ምንዳውም እዳው በእጃችን ነው፤ እዳውን የመቀነስ ምንዳውን የመጨመር ታሪካዊ ኀላፊነት ተጥሎብናል” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ
Next article“የፀጥታ መዋቅሩ በአስተማማኝ ቁመና ላይ ስለሚገኝ ባሕር ዳር ላይ የሚፈጠር ነገር አይኖርም” አቶ ደሳለኝ ጣሰው