“በአጣየ ከተማ የተጀመረው የሰላም ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁላችንም በጋራ እንድንሠራ ጥሪየን አቀርባለሁ” አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ.ር)

16

ባሕር ዳር: ነሐሴ 8/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተሞች ልማት ዘርፍ አሥተባባሪ እና የከተማ መሠረተ ልማት ቢሮ ኀላፊ አሕመዲን ሙሐመድ (ዶ.ር) በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የምትገኘውን የአጣየ ከተማ ጎብኝተዋል።

ባለፉት ዓመታት በአካባቢው በተፈጠሩ ግጭቶች ምክንያት ጉዳቶችን ያስተናገደችው የአጣየ ከተማ በቅርቡ ከመከላከያ ሠራዊት እና ከሕዝብ ጋር በተሠሩ ሥራዎች በከተማዋ አንጻራዊ ሰላም ስለመምጣቱም ተናግረዋል።

ዶክተር አሕመዲን ሙሐመድ ይኽ አንጻራዊ ሰላም እንዲሰፍን ዋጋ ለከፈሉ አካላት ከፍተኛ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልእክት “በአጣየ ከተማ የተጀመረው የሰላም ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሁላችንም በጋራ እንድንሠራ ጥሪየን አቀርባለሁ” ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበጥራት ተወዳዳሪ የኾኑ የሀገር ውስጥ ምርቶችን ለማምረት እየሠራ እንደሚገኝ የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ገለጸ።
Next articleግብር ከፋዮች ለአላስፈላጊ ቅጣት እና መጉላላት እንዳይዳረጉ ሕጉን ተከትለው በወቅቱ ግብራቸውን እንዲከፍሉ የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ አሳሰበ፡፡