“ውድ ባለተሰጥዖዎች፣ የኢትዮጵያችን ጥንካሬ በእናንተ እድገት ላይ የተመሠረተ ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)

15

ባሕር ዳር: ነሐሴ 6/2016 ዓ.ም (አሚኮ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልእክት በዛሬው ፈጣን ዓለም ባላሰለሰ ትምህርት እና የክህሎት እድገት ውስጥ መሳተፍ ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ እጅግ አስፈላጊ ኾኗል ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልእክታቸው በእረፍት ላይ ላላችሁ ተማሪዎች፣ ለወጣት ባለሞያዎች፣ ራሳቸሁን በእውቀት በመገንባት በሀገር ውስጥም ኾነ በውጭ በጎ ተፅዕኖ ለመፍጠር ለምትጓጉ ሁሉ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ፕሮጀክት ቀዳሚ ሊያደርጋችሁ ተሰናድቶላችኋል ነው ያሉት።

የትምህርት እና የእውቀት መነሻችሁ እና ያላችሁበት ደረጃ ምንም ይሁን ያላችሁን ክህሎት ለማሳደግም ኾነ አዲስ ነገር ለማወቅ ለምትሹ ሁሉ ሰፊ የእድል በር ተከፍቶላችኋል ብለዋል።

በመላው ኢትዮጵያ ያላችሁ የክህሎት አበልጻጊዎች፣ አሳዳጊዎች እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ይኽንን ፕሮጀክት እና እንቅስቃሴዎቹን እንዲደግፉ ጥሪ አቀርባለሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው “ውድ ባለተሰጥዖዎች፣ የኢትዮጵያችን ጥንካሬ በእናንተ እድገት ላይ የተመሠረተ ነው” ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበአማራ ክልል ለሻይ ቅጠል ምርት ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
Next article”የቴክኖሎጂ መራቀቅ ለሀሰተኛ መረጃዎች ሥርጭት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተገንዝቦ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል” የጋዜጠኝነት እና ሥነ-ተግባቦት መምህርት ሕይወት ዮሐንስ