የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል በጎንደር ከተማ ዳግም የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን እየተመለከቱ ነው፡፡

14

ባሕር ዳር: ነሐሴ 6/2016 ዓ.ም (አሚኮ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በሰጡት የሥራ አመራር በጎንደር ከተማ ዳግም የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን የሥራ እንቅስቃሴ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል እየተመለከቱ ነው፡፡

አሁን ላይ የመገጭ የመስኖ እና የመጠጥ ውኃ ግድብ ፕሮጀክት የሥራ እንቅሰቃሴን እየተመለከቱ ያሉት ሚኒስትሩ የአዘዞ ጎንደር የኮንክሪት አስፓልት መንገድ ሥራ እንቅስቃሴን እንደሚመለከቱም ይጠበቃል፡፡

እንደ ኢዜአ ዘገባ በከተማው የተጀመረውን የኮሪደር ልማት እና ዓለም አቀፍ ቅርስ የኾነውን የአጼ ፋሲል አብያተ መንግሥት የቅርስ ጥገና ሥራንም ከተመለከቱ በኋላ ሥለ ሥራው ሃሳባቸውን እንደሚያጋሩም ነው የተገለጸው፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበዞኑ ከሚገኙ ግብር ከፋዮች ውስጥ 85 በመቶ የሚኾኑት ከፍለው ማጠናቀቃቸውን የደቡብ ወሎ ዞን ገቢዎች መምሪያ ገለጸ።
Next article“አብሮነት እና ወንድማማችነት ብቸኛ መውጫ በራችን ነው፤ ያለአብሮነት ሀገር ማሻገር አይቻልም” የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አሕመድ አሊ