የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ለሥራ ጉብኝት ጎንደር ከተማ ገቡ።

60

ባሕር ዳር: ነሐሴ 6/2016 ዓ.ም (አሚኮ)የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ለሥራ ጉብኝት ዛሬ ጠዋት ላይ ጎንደር ከተማ ገብተዋል

ሚኒስትሩ ወደ ጎንደር ከተማ ሲገቡ የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ ደብሬ የኋላን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በአጼ ቴዎድሮስ አየር ማረፊያ አቀባበል ተደርጓላቸዋል።

ሚኒስትሩ በፌደራል መንግሥት እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ይመለከታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከጎንደር ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበኮምቦልቻ ከተማ ያለበቂ ምክንያት በተለያዩ እቃዎች ላይ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ ላይ የተወሰደው እርምጃ ተገቢ መኾኑን ነዋሪዎች ገለጹ።
Next articleየድህረ ምረቃ ፕሮግራም መግቢያ ፈተና እስከ ነሐሴ 10 ድረስ መራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡