ምሥጋና

15

🙏ዛሬ የምናመሠግናቸው ዶክተር ወልደመስቀል ኮስትሬን ነው
🙏ዶክተር ወልደመስቀል ኮስትሬ (1939 – 2008 ዓ.ም)
🙏 እ.አ.አ 1972 በጀርመን የሙኒክ ኦሎምፒክ ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ቡድን ዋና አሠልጣኝ ለነበሩት ንጉሤ ሮባ ምክትል አሠልጣኝ በመኾን ነበር ወደ አሠልጣኝነቱ ዓለም የገቡት
🙏በስፖርት ኮሚሽን በከፍተኛ ባለሞያነትም ሠርተዋል

🙏ከ1992 ባርሴሎና እስከ 2008 ቤጂንግ ኦሎምፒክ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ዋና አሠልጣኝ ኾነው አገልግለዋል
🙏ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ ስሟ ከፍ ብሎ እንዲጠራ ያደረጉትን የ5 ሺህ እና የ10 ሺህ ሜትር ባለድል አትሌቶች አፍርተዋል

🙏አሠልጣኝ ኾነው በተሳተፉባቸው አምስት የኦሎምፒክ ውድድሮች ለኢትዮጵያ 13 የወርቅ 5 የብር እና 10 የነሐስ በድምሩ 28 ሜዳሊያዎችን ማስገኘታቸው ተመዝግቦላቸዋል

🙏በ2006 ዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የዓመቱ ምርጥ አሠልጣኝ ብሎ ሸልሟቸዋል
🙏በስፖርት የ2007 ዓ.ም የበጎ ሠው ሽልማት አግኝተዋል

Previous articleየኮሌራ በሽታን ለመከላከል ከአጋር ተቋማት በጋር እየሠራን መኾኑን የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ጤና መምሪያ አስታወቀ።
Next article1 ሺህ 209 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።