ደቡብ ኮሪያ በሰብዓዊ እርዳታ ዙሪያ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በትብብር ለመሥራት ቁርጠኛ መኾኗን ገለጸች።

18

ባሕር ዳር: ነሐሴ 01/2016 ዓ.ም (አሚኮ)

የደቡብ ኮሪያ መንግሥት በኢትየጵያ ለሰብዓዊ እርዳታ የሚውል የ7 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል፡፡ ደቡብ ኮሪያ ያደረገችው ድጋፍ በዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች አማካይነት የሚሰራጭ መኾኑም ተገልጿል፡፡

ድጋፉ በግጭት ጉዳት ለደረሰባቸው እና ለችግር ተጋላጭ በኾኑ አካባቢዎች ለሚኖሩ የማኀበረሰብ ክፍሎች የሚውል ነው ተብሏል፡፡ እንደ ኤፍ ቢ ሲ ዘገባ ደቡብ ኮሪያ በሰብዓዊ እርዳታ ዙሪያ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በቅርበት እና በትብብር ለመሥራት ቁርጠኛ መኾኗንም አረጋግጣለች፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የአራት ከተማ አሥተዳደር ግብር ከፋዮች ግብራቸውን አጠናቅቀው ከፍለዋል” የምሥራቅ ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ
Next article“በወር አበባ ዙሪያ በተሠሩ ሥራዎች በርካታ ውጤቶች የተመዘገቡ ቢኾንም ሰፊ ጥረት የሚሹ ጉዳዮች አሉ” ያሉት ዶ/ር መቅደስ ዳባ