“የአራት ከተማ አሥተዳደር ግብር ከፋዮች ግብራቸውን አጠናቅቀው ከፍለዋል” የምሥራቅ ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ

14

ባሕር ዳር: ነሐሴ 01/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በምሥራቅ ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ እንዳለው የደጀን፣ የመርጦ ለማርያም፣ የሞጣ እና ግንደወይን ከተማ አሥተዳደር ግብር ከፋዮች ናቸው ግብራቸውን አጠናቅቀው የከፈሉት።

ሥራው እንዲሳካ ያልተቋረጠ ድጋፍ እና ክትትል ላደረጉ ለዞኑ መሪዎች፤ ለባለሙያዎች፣ በየደረጃው ለሚገኙ የከተማ አሥተዳደሮቹ መሪዎች፣ ለባለሙያዎች እና ያልተቋረጠ ድጋፍ ላደረጉ ባለድርሻ አካላት የዞኑ ገቢዎች መምሪያ ምሥጋና ማቅረቡን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article62 ሺህ እናቶች በጤና ተቋማት መውለዳቸውን የደቡብ ወሎ ዞን ጤና መምሪያ ገለጸ።
Next articleደቡብ ኮሪያ በሰብዓዊ እርዳታ ዙሪያ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በትብብር ለመሥራት ቁርጠኛ መኾኗን ገለጸች።