ጎንደር ከተማ እስራኤል ካሉ እህት ከተሞች ጋር ያላትን ግንኑነት ለማጠናከር ያለመ ምክክር ተካሄደ፡፡

69

ባሕር ዳር: ነሐሴ 01/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ከእስራኤል ምክትል አምባሳደር ቶመር ባርላቪ ጋር በቱሪዝም፣ የእህትማማች ከተሞችን ለማጠናከር እና የልማት እንቅስቃሴዎችን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር አድርጓል። የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ባዩህ አቡሃይ ከእስራኤል ምክትል አምባሳደር ጋር በቱሪዝም ዘርፍ፣ በሌሎች የልማት የሥራ እንቅስቃሴዎችን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ሰፊ ውይይት ማድረጋቸው ነው የተገለጸው።

ምክክሩ ጎንደር ከተማ እስራኤል ካሉ እህት ከተሞች ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ መኾኑ ተገልጿል። የከተማ አሥተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ባዩህ አቡሃይ፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የሕዝብ ግንኙነት እና አደረጃጀት ዋና አማካሪ ቻላቸው ዳኘው እና በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አሥተዳደሩ የመሠረተ ልማት ዋና ሥራ አሥኪያጅ አንዱዓለም ሙሉ መሳተፋቸውን ከጎንደር ከተማ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የዳኝነት ሥርዓትን በማሻሻል የዜጎችን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መንገድ ቃኝቶ ወደ ተሻለ ደረጃ ማድረስ ያስፈልጋል” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ
Next article62 ሺህ እናቶች በጤና ተቋማት መውለዳቸውን የደቡብ ወሎ ዞን ጤና መምሪያ ገለጸ።