“108 ሚልዮን ብር ትርፍ ማስመዝገብ የቻልንበት ስኬታማ ዓመት ነበር” የጎሽ ሜዳ ቧንቧ እና ፕላስቲክ ማምረቻ ድርጅት

25

ደሴ: ሐምሌ 30/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በደሴ ከተማ የሚገኘው የጎሽ ሜዳ ቧንቧ እና ፕላስቲክ ማምረቻ ድርጅት ከድርጅቱ መሪዎች እና ሠራተኞች ጋር ዓመታዊ የሠራተኞች ቀንን በማክበር፣ የ2016 ዓ.ም የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2017 ዓ.ም ዕቅድ ትውውቅ አካሂዷል። በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ጠንካራ ሥራዎች እና በቀጣይ በጀት ዓመት ቢስተካከሉ የተባሉ ሀሳቦች በሪፖርት ተመላክተዋል።

የድርጅቱ ሠራተኞች በበጀት ዓመቱ የተከናወኑት ተግባራት ውጤታማ እንደነበሩ ገልጸዋል፡፡ እንደ ችግር የሚነሱት የመለዋወጫ ችግሮች መፍትሄ ማግኘት ከተቻለ በ2017 ዓ.ም ከዚህ የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚቻልም ነው ያስረዱት። የጎሽ ሜዳ ቧንቧ እና ፕላስቲክ ማምረቻ ድርጅት ዋና ሥራ አሥኪያጅ በረደድ ተሰማ “በ2016 በጀት ዓመት 108 ሚልዮን ብር ትርፍ ማስመዝገብ የተቻለበት ስኬታማ ዓመት ነበር” ነው ያሉት።

በመድረኩ በ2016 ዓ.ም ከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም ለነበራቸው የድርጅቱ ሠራተኞች የዕውቅና እና ሽልማት መርሐ ግብርም ተካሂዷል።

ዘጋቢ፡- ፊኒክስ ሀየሎም

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleመገናኛ ብዙኃን ለኀብረተሰቡ ወቅታዊ እና የጠራ መረጃ በማድረስ ለሰላም እና ለአብሮነት መጠናከር ቅድሚያ ሰጥተው እንዲሠሩ ተጠየቀ፡፡
Next articleበክልል ከ437 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ አምራች ኢንዱስትሪዎች መስተናገዳቸውን ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለጸ።