“ከተምሳሌታዊዋ የምድር ጌጥ፣ ከተፈጥሮ ኀያል ግርማ ሞገሰ ማሳያዋ ምድር ባሕር ዳር ገብተናል” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ

70

ባሕር ዳር: ሐምሌ 25/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ “ባሕር ዳር ውብ ብቻ አይደለችም፤ ውበት ናት!” በሚል ገልጸዋታል። ዛሬ በከተማዋ የሚገኘውን የባህር ዳር ስታዲየም ያለበትን ደረጃ ተመልክተናል ብለዋል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ስታዲየሙ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ውድድሮችን ማስተናገድ እንዲችል ተድረጎ እየተገነባ እንደሚገኝም ነው የገለጹት፡፡

በግንባታ ምዕራፍ የመጨረሻ ደረጃ ላይ የሚገኘው ስታዲየሙ በቀጣይ ዓመት ግንባታው ተጠናቅቆ ጨዋታዎችን ማስተናገድ እንዲችል ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡

አቶ ተመስገን በቆይታችንም በባሕር ዳር ስታዲየም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አካሂደናል ብለዋል በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባጋሩት መልእክት።

በባሕርዳር ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ልባዊ አቀባበል ላደረጉልን የአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች ብሎም ለከተማዋ ከንቲባ እና ሕዝብ ላቅ ያለ ምሥጋና አቀርባለሁ ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደረሰው የመሬት ናዳ ለተጎዱ ወገኖች ሁለት ሚሊዮን ብር ዋጋ ያለው የስንዴ ዱቄት ድጋፍ አደረገ።
Next articleየአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ በስኬት መጠናቀቁን የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋየ አስታወቁ፡፡