የአማራ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቀቀ።

499

ባሕር ዳር: ሐምሌ 25/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ በሦስተኛ ቀን ውሎው የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቅቋል። ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ያቀረቡትን ሹመት የምክር ቤቱ አባላት መርምረው አጽድቀዋል።
በዚህም፦
1. አቶ ዓለምአንተ አግደው ወንድሜነህ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት
2. ሙሉዓለም ቢያዝን ዓለሙ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት
3. አቶ መልካሙ ፀጋየ ገላው የባሕል እና ቱሪዝም ቢሮ ኀላፊ ኾነው ተሹመዋል።
በተጨማሪም በክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አማረ ሰጤ የቀረቡ የቋሚ ኮሚቴ አባላት ለምክር ቤቱ ቀርቦ ጸድቋል።
1. የሰው ሃብት አሥተዳደር እና ቱሪዝም ልማት ቋሚ ኮሚቴ ሠብሣቢ አበራ ፋንታው
2. የመንግሥት ወጪ ቁጥጥር ቋሚ ኮሚቴ ሠብሣቢ እመቤት ከበደ ኾነው ተሹመዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ ክልል የ2017 በጀት 150 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ኾኖ ጸደቀ፡፡
Next articleሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደረሰው የመሬት ናዳ ለተጎዱ ወገኖች ሁለት ሚሊዮን ብር ዋጋ ያለው የስንዴ ዱቄት ድጋፍ አደረገ።