ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና መንግሥታቸው የጎንደርን የረጅም ጊዜ የልማት ጥያቄ መመለሳቸውን እውቅና የሚሰጥ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

97

ጎንደር: ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በጎንደር ከተማ መንግሥት ለልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ያሳየውን ቁርጠኝነት የሚደግፍ እና ያሉ ችግሮች ተሻሽለው አስተማማኝ ሰላም እንዲመጣ የሚጠይቅ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

“ለሰላም ዘብ እንቆማለን፤ የተጀመሩ ልማቶችን እናስቀጥላለን” በሚል መሪ ሃሳብ በድጋፍ ሰልፉ ሕዝቡ ዘላቂ ሰላም እና ልማትን ለማምጣት የሚያደርገውን ጥረት እንደሚያስቀጥል ተመላክቷል።

በሰላማዊ ሰልፉ “የጎንደር እና አካባቢው የረጅም ጊዜ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን፣ እሳቸው የሚመሩት ፖርቲ እና መንግሥት ያሳዩንን ቁርጠኝነት እውቅና እንሰጣለን” የሚሉና ሌሎች ሃሳቦች እየተገለጹ ነው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የሕዝባችንን ችግሮች መፍታት የሚችሉ የተለያዩ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ሥርዓቶችን በማበልፀግ መጠቀም ይገባናል” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ
Next article“ካውንስሉ ከየትኛውም ወገን ጣልቃ ገብነትን ሳያስተናግድ ሁለቱ ወገኖች ወደሰላም እንዲመጡ ይሠራል” የሰለም ካውንስሉ ዋና ሰብሳቢ ቆሞስ አባ ዩሴፍ ደስታ