የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ከኢራን የወጣቶች ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።

15

ባሕር ዳር: ሐምሌ 19/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ፉአድ ገና ከኢራን የወጣቶች ሚኒስትር ዴኤታ ሲና ካልሆር ጋር ተወያይተዋል።

በኢትዮጵያና በኢራን ወጣቶች መካከል ድልድይ የሚኾን መደላደል ማመቻቸት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውም ተገልጿል።

በውይይታቸውም በአይሲቲ፣ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ላይ በትብብር ለመሥራት ተስማምተዋል።

የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ፉአድ ገና ከብሪክስ የወጣቶች ጉባኤ ጎን ለጎን ከብሪክስ አባል ሀገራት የወጣት ሚኒስትሮች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት እያደረጉ እንደሚገኙ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ካውንስል የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በፓርኮቻችን የኢትዮጵያንና የሩሲያን የረጅም ጊዜ ግንኙነት የሚመጥን የሩሲያ ኢንቨስትመንት እንዲኖር እንፈልጋለን” ፍስሃ ይታገሱ (ዶ.ር)
Next articleለ3 ቀናት የሚቆይ ብሔራዊ ሐዘን ታወጀ።