በላይ አርማጭሆ ወረዳ የተገነባው ተንጠልጣይ ድልድይ ለአገልግሎት ክፍት ኾነ፡፡

22

ባሕር ዳር: ሐምሌ 18/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በላይ አርማጭሆ ወረዳ የረጅም ጊዜ የኅብረተሰብ ጥያቄ የነበረው የድልድይ ግንባታ ጥያቄ ምላሽ አግኝቷል፡፡

ማህና በተሰኘ ወንዝ ላይ የተገነባው የተንጠልጣይ ድልድይ 120 ሜትር ርዝመት ያለው ነው፡፡ ድልድዩ የኅብረተሰቡ የረዥም ጊዜ ጥያቄ የነበረ ሲኾን ለአገልግሎት በመብቃቱ ኅብረተሰቡ መደሰቱን ገልጿል፡፡ ይህ የእግረኛ ተንጠልጣይ ድልድይ በወረዳው ሰባት ቀበሌዎችን እንደሚያገናኝ ነው የተገለጸው፡፡
ግንባታው በክልሉ መንገድ ቢሮ፣ ሄልቬታስ በተሰኘ መንግሥታዊ ባልኾነ ድርጅት እና በኅብረተሰቡ ተሳትፎ ነው የተገነባው፡፡

ተንጠልጣይ ድልድዩ መገንባቱ ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሚኖረው ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ፋይዳ የጎላ እንደኾነ ከማዕከላዊ ጎንደር ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመሬት ናዳ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ።
Next articleከ249 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ግብርና መምሪያ አስታወቀ።