የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከተመድ ምክትል ዋና ጸሐፊ ጋር ተወያዩ።

15

ባሕር ዳር: ሐምሌ 16/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ምክትል ዋና ጸሐፊ አሚና መሀመድ ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ የኢትዮጵያ የልማት እንቅስቃሴና የአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ መሆኑ ተመላክቷል።
በተጨማሪም መጪውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጉባኤ አስመልክቶ መምከራቸው ተገልጿል።

አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ምክትል ዋና ጸሐፊዋ በተመድ የልማት ሥርዓት ውስጥ እያበረከቱት ስለሚገኘው የአመራርነት ሚና ምድጋና ማቅረባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleቺርቤዋ አምሊ 15/2016 ም.አሜት
Next articleኢትዮጵያ ሴቶች ወደ አመራር ሰጪነት እንዲመጡ ውጤታማ ሥራ እየሠራች መኾኑን የተመድ ምክትል ዋና ጸሐፊ አሚና ሙሐመድ ገለጹ።