ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ጋር ተወያዩ።

25

ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 15/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ጋር ተወያዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በሚያዚያ ወር ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ጋር በመገናኘት በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገን ነበር ብለዋል። በወቅቱም በየደረጃው ውይይቶች እንዲቀጥሉ አቅጣጫ ተቀምጦ እንደነበርም ጠቅሰዋል።

ዛሬ የሚያዚያው ውይይታችን ቀጣይ የሆነና ሁሉን አቀፍ ጠቀሜታ ባላቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መግባባት መፍጠርን የተመለከተ ውይይት አድርገናል ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየታዳጊ ሀገራት የልማት ጥያቄ ሊደመጥ እና ምላሽ ሊሰጠው እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ታዬ አጽቀሥላሴ ጠየቁ።
Next article“የአካባቢን ውበት ለመጠበቅ እና መልካም ሥነ ምህዳር ለመፍጠር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አይተኬ ሚና አለው” ከንቲባ መንበሩ ዘውዴ