“በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ ተገኝቼ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ላይ በመሳተፌ ተደስቻለሁ” የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ

46

ባሕር ዳር: ሐምሌ 13/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በጎንደር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መኾኑን የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ባዩህ አቡሃይ ገልጸዋል፡፡

የኮሪደር ልማቱ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ከንቲባውን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በሥራዉ እየተሳተፉ የሚገኙ ባለሙያዎችን እና ሠራተኞችን እያበረታቱ ነው።

በጎንደር ከተማ ከሰዓት በፊት በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ዘርፍ ዘርፍ አስተባባሪ እና የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኀላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ.ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡

አቶ አሕመድ ሽዴ በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ተገኝተው በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በመሳተፋቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።

ዘጋቢ፡- አዲስ አለማየሁ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበራያ ቆቦ ወረዳ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር እየተከናወነ ነው።
Next article“የብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና የሥነ-ምግባር ኮሚሽን ተቋማዊ አቅምን ለማጠናከር በተደረገው ሥራ ውጤት አስመዝግቧል” አቶ አደም ፋራህ