ከባሕር ዳር ኮምቦልቻ እና ከኮምቦልቻ ባሕር ዳር በረራ ሊጀመር ነው።

41

ባሕር ዳር: ሐምሌ 11/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ተቋርጦ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኮምቦልቻ ወደ ባሕር ዳር እና ከባሕር ዳር ወደ ኮምቦልቻ በረራ ሊጀመር መኾኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮምቦልቻ ቅርንጫፍ አስታውቋል፡፡

ከኮምቦልቻ ኮሙዩኬሽን ባገኘነው መረጃ መሰረት ተቋርጦ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኮምቦልቻ ወደ ባሕር ዳር እና ከባሕር ዳር ወደ ኮምቦልቻ በረራ በመጪው ቅዳሜ ሐምሌ13/2016 ዓ.ም ዳግም እንደሚጀምር ለማወቅ ተችሏል።

በአዲስ መልክ የሚጀመረው በረራ በየቀኑ የሚካሄድ መኾኑም ታውቋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleከቴክኖሎጂ ማስፋፋት ባለፈ በአረንጓዴ አሻራ ሥራ ለ4 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ወደ ሥራ መግባቱን ኢትዮ ቴሌኮም ገለጸ፡፡
Next articleየከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ለሀረሪ ክልል ለተለያዩ የልማት ሥራዎች የሚውል የ 20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ።