“በአዲስ ከቀረበው ሰው ሠራሽ ማዳበሪያ ውስጥ 94 በመቶ ያህሉ ለአርሶ አደሮች ተሰራጭቷል” የምሥራቅ ጎጃም ዞን

48

ባሕር ዳር: ሐምሌ 11/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በምሥራቅ ጎጃም ዞን በበጀት ዓመቱ ግዥ ከተፈጸመለት ሰዉ ሠራሽ የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የሚኾነዉ ወደ ዞኑ መድረሱን አስታውቋል።

የምሥራቅ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አበበ መኮነን እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ በአዲስ ለማቅረብ ግዥ ከተፈጸመለት 1 ሚሊዮን 544 ሺህ 956 ኩንታል ሰው ሠራሽ ማዳበሪያ ውስጥ 1 ሚሊዮን 159 ሺህ 632 ኩንታል ያህሉ ወደ ዞኑ መግባቱን ተናግረዋል።

እስካሁን ለዞኑ ከቀረበዉ ሰው ሠራሽ ማዳበሪያ ውስጥ 1 ሚሊዮን 74 ሺህ ኩንታል በላይ ለአርሶ አደሩ እንዲሰራጭ መደረጉን አቶ አበበ ገልጸዋል።

በአዲስ ከቀረበው ሰው ሠራሽ ማዳበሪያ ውስጥ 94 በመቶ ያህሉ ለአርሶ አደሮች መሰራጨቱም ተገልጿል።

የምሥራቅ ጎጃም ዞን በ2016/17 የምርት ዘመን ከ612 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በሰብል በመሸፈን ከ23 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት አቅዶ እየሠራ መኾኑንም ከክልሉ ኮሙኒዩኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“አረንጓዴ አሻራ ለነገው ትውልድ የተስፋ እስትንፋስ ነው” የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ቢክስ ወርቄ
Next articleየባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ እንዲጠናቀቅ የሴቶች፣ ህጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ፡፡