“የሕዝባችንን ፍላጎት ለማሟላት በየትኛዉም ጊዜ እና አጋጣሚ ችግሮቻችን በውይይትና በድርድር እንድንፈታ በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ አድርገናል” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ

22

ባለፉት ወራቶች በክልላችን ሕዝብ ላይ የደረሰዉን ስቃይ እኛም ሆነ ጫካ ያሉ ወንድሞቻችን ያዉቁታል፡፡ አሁንም በድጋሜ ለማረጋገጥ የምፈልገዉ ለሰላማዊ አማራጮች በሙሉ በራችን ክፍት ስለመሆኑ ነው፡፡

በመሆኑም ለሕዝባችን ሰላም እና አንድነት፤ ለክልላችን ልማት እና እድገት ስንል በየትኛዉም ቦታ እና ሁኔታ፣ በማንኛዉም አማራጭ ለመወያየት እና ለመደራደር ዝግጁ ነን።

ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ

🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊

Previous article“በተመረቅንበት የትምህርት መስክ ሥራ ፈጣሪ በመኾን ሀገርን የሚጠቅም ሥራ እንሠራለን” ተመራቂዎች
Next article“ግጭቱ የዜጎቻችንን ሕይወት አሳጥቶናል፤ በርካታ ቁሳዊ ውድመት ከማስከተል ውጪ ያተረፈልን አንዳችም ነገር የለም” ከንቲባ መንበሩ ዘውዴ