“የሰላም ካውንስሉ መቋቋሙ በጣም አስፈላጊ እና ጠቃሚ በመኾኑ አስፈላጊውን ሁሉ እገዛ እናደርጋለን” የሀራ ከተማ የመንግሥት ሠራተኞች

43

ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 02/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በሀራ ከተማ አሥተዳደር “ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም” በሚል መሪ ሀሳብ ከመንግሥት ሠራተኞች ጋር ኮንፈረንስ ተካሄዷል።

የሀራ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ሙሐመድ ስዒድ ሰላም ለሁሉም መሰረት በመኾኑ ሁላችንም ለሰላም በትኩረት ልንሠራ ይገባል ብለዋል። ከንቲባው አያይዘውም ማንኛውም ጥያቄ የሚመለሰው በሰላማዊ መንግድ በመኾኑ ሁሉም አካል ለሰላም ካውንስሉ ጥሪ መልካም ምላሽ ሊኖረው እንደሚገባ አመላክተዋል።

የኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የሰላም ካውንስሉ መቋቋሙ በጣም አስፈላጊ እና ጠቃሚ መኾኑን ገልጸዋል። በመኾኑም አስፈላጊውን ሁሉ እገዛ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበሰሜን ወሎ ዞን ጋዞ ወረዳ “ሰላም ለሁሉም፣ ለሁሉም ሰላም” በሚል መሪ መልእክት ከመንግሥት ሰራተኞች ጋር ወይይት ተካሄደ፡፡
Next articleበባቲ ወረዳ በሰላጤ ቀበሌ ‘ሚአ’ ወንዝ ላይ የተገነባ ተንጠልጣይ ድልድይ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።