በአላማጣ ከተማ የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይል አባላት ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አካሄዱ፡፡

16

ባሕር ዳር: ሐምሌ 2/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን አላማጣ ከተማ የተደረገው ውይይት በአካባቢው ስላለው ወቅታዊ የሰላም ሁኔታ እና ተፈናቅለው የነበሩ ነዋሪዎችን ወደ ቀያቸው በሚመለሱበት ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው።

የሪፐብሊኩ ጥበቃ ኃይል ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ብርጋዲየር ጄኔራል በላይ አየለ ተፈናቅለው የነበሩ የአላማጣ ወረዳ ነዋሪዎች ወደ ቤት ንብረታቸው በመመለስ ሰላማዊ ሕይዎታቸውን ማስቀጠል እንደሚገባቸው ተናግረዋል፡፡

የአካባቢው ነዋሪዎች እና የሃይማኖት አባቶች በበኩላቸው የሪፐብሊካን ጥበቃ ኃይል እና ሌሎችም የጸጥታ አካላት ወደ ስፍራው ከተሠማሩ በኋላ አካባቢው ፍጹም ሰላም መኾኑን ገልጸዋል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየክልሉ የሰላም ካውንስል ባቀረበው የሰላም ጥሪ መሰረት 20 ታጣቂ ኃይሎች ማኅበረሰቡን ተቀላቀሉ።
Next articleሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያ ባለፋት ዘመናት ያልተጠቀመችበትን መልካም አጋጣሚ እንድትጠቀምበት እድል የፈጠረ መኾኑን አምባሳደር መሐሙድ ድሪር ተናገሩ።