
ባሕር ዳር: ሐምሌ 02/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በታች አርማጭሆ ወረዳ የክልሉ የሰላም ካውንስል ባቀረበው የሰላም ጥሪ መሰረት 20 ታጣቂ ኃይሎች ማኅበረሰቡን ተቀላቅለዋል።
ተጣቂዎቹ ለተደረገላቸው የሰላም ጥሪ መንግሥትን አመስግነው በቀጣይ ከመንግሥት ጎን ተሰልፈው መደበኛ ሥራቸውን እንደሚጀምሩ ገልጸዋል። ሌሎች አካላትም መንግሥት ያመቻቸውን የሰላም ጥሪ ተቀብለው እንዲገቡ ጥሪ ማቅረባቸውን የማዕከላዊ ጎንደር ኮሙኒኬሽን መረጃ ያሳያል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!