በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሰላም ጥሪውን የተቀበሉ ታጣቂዎች ወደ መደበኛ ሕይዎታቸው እንደሚመለሱ ተናገሩ።

17

ባሕር ዳር: ሐምሌ 2/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሰላም አማራጩን የሚቀበሉ ታጣቂዎች ቁጥር እየጨመረ ነው።

በዞኑ ላይ አርማጭሆ ወረዳ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 10 ታጣቂዎች የሰላም አማራጩን ተቀብለው ማኅበረሰቡን ተቀላቅለዋል። መንግሥት ላደረገላቸው ይቅርታ ያመሰገኑት ታጣቂዎቹ በቀጣይ ወደ መደበኛ ሕይዎታቸው ተመልሰው የአካባቢያቸውን ሰላም እና ልማት ለማረጋገጥ እንደሚሠሩም ተናግረዋል።

እንደ ማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሐንግሥት ኮምዩኒኬሽን መምሪያ መረጃ ወደ ሰላማዊ ሕይዎት የተመለሱት ታጣቂዎች የሚፈጠሩ ችግሮችን በውይይት መፍታት የስልጣኔ አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የታሪክም የትውልድም ተወቃሽ ላለመኾን ጦርነት ይብቃን” በምዕራብ ጎንደር ዞን የገንዳ ውኃ ከተማ አሥተዳደር የመንግሥት ሠራተኞች።
Next articleልዩነት አለን የሚሉ ሁሉ ወደ ውይይት እንዲመጡ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ጠየቁ፡፡