የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ እየገቡ ነው።

53

ባሕር ዳር: ሰኔ 30/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን የሚወስዱ ተማሪዎች ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መግባት ጀምረዋል።

በዚህ ዓመት በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ 5 ሺህ 562 ተማሪዎች ተገኝተው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን እንደሚወስዱ ታውቋል።

ፈተናውን ከሚወስዱ ተማሪዎች መካከል 3 ሺህ 311 ሴቶች መኾናቸው ነው የተብራራው።

የሰሜን ሽዋ ዞን ትምህርት መምሪያ በወሎ ዩኒቨርሲቲ ኮምቦልቻ ካምፖስ ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎች እንዳሉም ገልጿል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ሞት ይበቃናል! ለሰላም መስፈን ልንቆም ይገባናል” የሰላም ተወያዮች
Next article“ሰላም፣ ፍቅር እና አንድነት ኢትዮጵያን ያሻግራሉ” አቶ ብናልፍ አንዷለም