“የብዙ ምንጮች መፍለቂያ፣ የድንቅ ተፈጥሮ መገኛ፣ የእምቅ የቱሪዝም ባለቤት፣ የሀገር ሽማግሌዎች ምድር አርባ ምንጭ!” ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ

56

ባሕር ዳር፡ ሰኔ 29/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባጋሩት መልእክት “የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል የጀመርነውን የዘንድሮውን የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአርባ ምንጭም ቀጥለናል ብለዋል፡፡

በዚህ መርሐ ግብር መትከል ብቻ ሳይሆን የተከልናቸውን በመከታተልና በመንከባከብ ዛፍ ሆነው ከሚሰጡት ውበት በተጨማሪ ፍሬ እንዲያፈሩ መሥራት ይጠበቅብናል ነው ያሉት፡፡

የአርባ ምንጭ ሕዝብ ላደረገልን የሞቀ አቀባበል እናመሠግናለን ብለዋል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሀገር በቀል ችግኞች ይተከላሉ።
Next articleየአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ5 ሺህ 900 በላይ ተማሪዎቹን አስመረቀ።