“አርባ ምንጭ በተለያዩ የፍራፍሬ ዛፎች፣ ድንቅ አዕዋፍ፣ አስደማሚ ተራሮች፣ የውኃ ምንጮች እምቅ ሀብት የታደለ እጅግ ተፈላጊ መዳረሻ ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ.ር)

29

ባሕር ዳር፡ ሰኔ 29/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በአርባ ምንጭ የተፈጥሮ ስጦታው ታላቅ ተስፋን የመጫሩን ያህል የአካባቢውን ምሉዕ አቅም ለመጠቀም የሠራነው ጥቂት በመሆኑ ደግሞ ያስቆጫል ሲሉ ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የ’ገበታ ለትውልድ’ ፕሮጀክት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዚህ “የምድር ገነት” ድርሻ በመግዛት ኢንቨስት ለማድረግ እድል አቅርቧል ነው ያሉት በመልዕክታቸው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ፅንፈኝነት ብሔር የለሽ የቅን ልቦች ሰባሪ ነው”
Next article“ከተማችን ለመኖር የምትመች እና አረንጓዴ የምትለብስ የምናረጋት እኛ ነን፤ ለዚህም ነው ችግኝ የምንተክለው” ከንቲባ አዳነች አቤቤ