
ባሕር ዳር: ሰኔ 27/2016 ዓ.ም (አሚኮ)ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በምክር ቤቱ 36ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከእንደራሴዎች ለሚቀርብላቸው ጥያቄ ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመደበኛ ስብሰባው የ2016 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት እና በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 36ኛ መደበኛ ስብሰባ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ይጀምራል። የስብሰባውን ሂደት አሚኮ በሁሉም አማራጮች በቀጥታ እየተከታተለ ያስተላልፋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!