የትራንስፖርት ዘርፉ በአዳዲስ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የታገዘ እንዲኾን ሥራዎች እየተሠሩ መኾኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ገለጸ።

39

አዲስ አበባ: ሰኔ 26/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የያዘችውን ዕድገት ለማፋጠን ሥራዎች እየተሠሩ መኾኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ.ር) ገልጸዋል፡፡ በሀገሪቱ ቀልጣፋ፣ ምቹ እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ሥርዓት እንዲኖር ለማድረግ ሥራዎች በስፋት መሠራታቸውን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከአውቶ ቴክ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ በአውቶሞቲቨ ኢንዱስትሪ ላይ ያተኮረ አውቶሞቲቭ ትራንስፖርት ኤክስፖም በሚሊኒየም አዳራሽ ተከፍቷል። ኤክስፖው ከሰኔ 26/2016 ዓ.ም እስከ ሰኔ 28/2016 ዓ.ም እንደሚቆይ ነው የተገለጸው።

በዚህ አውቶሞቲቨ ትራንስፖርት ኤክስፖ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች፣ በትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ዘርፍ የተሰማሩ ባለ ሃብቶች፣ የካምፓኒ ተወካዮች እና የሥራ ፈጣሪ ወጣቶች ታዳሚ ኾነዋል።

ዘጋቢ፡- ሰለሞን አሰፌ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የጸጥታ መደፍረስ ዘርፉን ክፉኛ እንደጎዳው ገለጸ፡፡
Next article“ያለንን ሃብት ተጠቅመን ከኅብረተሰቡ ጋር በቅንጅት በመሥራት በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ይገባናል” አቶ ወርቁ ሃይለማርያም