የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ በጅቡቲ የዶራሌ ሁለገብ ወደብን ገበኙ።

18

ባሕር ዳር: ሰኔ 26/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በጅቡቲ የዶራሌ ሁለገብ ወደብ ተገኝተው የኢትዮጵያ አጠቃላይ የገቢ-ወጪ የዝውውር ሂደቱን ተመልክተዋል። በመስክ ምልከታቸውም የዘንድሮ የአፈር ማዳበሪያ ኦፕሬሽን ሂደትን ተዘዋውረው ጎበኝተዋል።

በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ማኀበራዊ ትስስር ገጽ እንዳሰፈረው ሚኒስትሩ በታጁራ ወደብ ተገኝተው ወደ ኢትዮጵያ የሚደረገውን የድንጋይ ከሰል ዝውውር ሂደትም ተመልክተዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article”የሃይማኖት አባቶች የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም እና አንድነት ለማረጋገጥ የላቀ አስተዋጽኦ አላቸው“ የሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዱዓለም
Next articleበክልሉ ያጋጠመውን የጸጥታ ችግር ለመቀልበስ እና መንግሥታዊ መዋቅርን ለማጠናከር በትኩረት እየተሠራ መኾኑን የአማራ ክልል ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡