
ደብረ ብርሃን: ሰኔ 25/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ የሸዋ ቀጣና የሁለት ወራት የመስክ ስምሪት የአፈጻጸም ግምገማ እና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በደብረ ብርሃን ከተማ እየተካሄደ ነው።
በውይይት መድረኩ ላይ የኮማንዶ እና አየር ወለድ እዝ ምክትል አዛዥ እና የሰሜን ሸዋ ኮማንድ አስተባባሪ ብርጋዴር ጀኔራል አበባው ሰይድ፣ የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኀላፊ በሪሁን መንግሥቴ፣ የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ መካሻ አለማየሁ እና ሌሎች የዞን እና የወረዳ መሪዎች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፦ ደጀኔ በቀለ
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!