“ማኅበረሰብን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ምርምሩን፣ የማኅበረሰብ አገልግሎቱንና የቴክኖሎጅ ሽግግሩን ከግብርና ሥራ ጋር አብረን ማስኬድ አለብን” ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ.ር)

12

ባሕር ዳር፡ ሰኔ 25/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 6ኛ ዓመት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በተዘጋጀው የመትከያ ቦታ የአፕልና የደጋ ቡና ችግኝ በመትከል ተጀምሯል፡፡ መርሐ-ግብሩን ያስጀመሩት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ.ር) “ግብርናና አረንጓዴ ልማትን ስናካሂድ የነበረው ራቅ ወዳሉ አካባቢዎችና ወደ ወረዳዎች በመሄድ የነበረ ሲሆን፣ አሁን ግን ችግኝ ከማፍላት ጀምሮ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላን ከግቢያችን ጀምረናል” ብለዋል።

ፕሬዘዳንቱ ግብርናና አረንጓዴ ልማት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የትኩረት መስክ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ “የኢትዮጵያ፣ የክልላችን ብሎም የአካባቢያችን የኑሮ መሰረት ግብርና በመሆኑ የአካባቢውን ማኅበረሰብ ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ምርምሩን፣ የማኅበረሰብ አገልግሎቱንና የቴክኖሎጅ ሽግግሩን አብረን ማስኬድ አለብን” ያሉት ፕሬዘዳንቱ ዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ ግብርናና አረንጓዴ ልማትን እያሰፋና እየሠራ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የትራፊክ እንቅስቃሴው ጤናማ እንዲኾን ማኅበረሰቡ በባለቤትነት መተባበር አለበት” የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት መምሪያ
Next articleአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) በደም ልገሳ ላበረከተው አስተዋጽኦ እውቅና እና ምስጋና አገኘ።