“በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ሃሳብ የ2016 ዓ.ም ሀገር አቀፉ የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።

77

አዲስ አበባ: ሰኔ 12/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በመርሐ ግብሩ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ ሚኒስትሮች፣ በጎ ፈቃደኞች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችም ተገኝተዋል። በዘንድሮው የክረምት ወራት በ14 ዘርፎች ከ34 ሚሊዮን በላይ በጎ ፈቃደኞች የሚሳተፉ ሲኾን ከ49 ሚሊዮን በላይ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነውም ተብሏል።

በዘንድሮ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሥራ ድግግሞሽን እና የሃብት ብክነትን ማስቀረት ትኩረት እንደሚሰጠው የተገለፀ ሲኾን በገንዘብ ሲተመን 26 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ አገልግሎት ለመስጠት መታቀዱም ተገልጿል። የንቅናቄ መድረኩን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ፣ የሰላም ሚኒስቴር እና የትምህርት ሚኒስቴር በጋራ እንዳዘጋጁትም ተገልጿል።

ዘጋቢ፦ ቤተልሄም ሰለሞን

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ታጣቂ ኃይሎች ለትጥቅ ያበቃቸውን አጀንዳ ወደ ሀገራዊ ምክክሩ ቢያቀርቡት ሁሉም አሸናፊ መኾን ይችላል” ኢዜማ
Next article“ሕዝቡ በፀጥታ ችግሩ ከፍተኛ ጫና እንደደረሰበትና ሕግ እና ሥርዓት እንዲከበርለት አጥብቆ እንደሚሻ ተገንዝበናል።” የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ከፋለ ሙላቴ