1 ሺህ 445ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል አድሃ ዓረፋ በዓል በኮምቦልቻ ከተማ ተከብሯል።

13

ባሕር ዳር: ሰኔ 09/2016 ዓ.ም (አሚኮ)1ሺህ 445ኛው የዒድ አል አድሃ ዓረፋ በዓል በኮምቦልቻ ከተማ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች ተከብሯል።

በበዓሉ ላይ የኮምቦልቻ ከተማ እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሼህ አሕመድ አወል፣ የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ መሐመድአሚን የሱፍን ጨምሮ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች እና የሃይማኖቱ ተከታዮች በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።

የኮምቦልቻ ከተማ እስልምና ጉዳይ ምክር ቤት ሰብሳቢ ሼህ አሕመድ አወል የዓረፋ በዓልን ስናከብር የተቸገሩትን በመርዳት እና ሃይማኖቱ በሚያዘው መሠረት ሊኾን እንደሚገባ አሳስበዋል።

የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ መሐመድአሚን የሱፍ በበኩላቸው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ከኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ማኅበራዊ ትስስር ገጽ እንዳገኘነው መረጃ ከንቲባው የዓረፋ በዓልን ስናከብር ሰላም እንዲሰፍን ዱዓ በማድረግ እንዲሁም በዓሉን ስናከብር የተቸገሩ ወገኖችን በመደገፍ ሊኾን ይገባል ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ሕዝበ ሙስሊሙ የዒድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓልን ሲያከብር የቆየውን የመረዳዳት እና የአብሮነት እሴቱን የበለጠ በማጠናከር ሊኾን ይገባል” የምሥራቅ ጎጃም ዞን ሸሪዓ ፍርድ ቤት ዳኛ ሼህ ወለላው ሰይድ
Next articleየዒድ ሰላት ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ መጠናቀቁን የጸጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ፡፡