“ሕዝበ ሙስሊሙ የዒድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓልን ሲያከብር በአብሮነት እና በመረዳዳት መንፈስ ሊኾን ይገባል” አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ

11

ባሕር ዳር: ሰኔ 08/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ የዒድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አፈ-ጉባኤዋ ለመላው የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1 ሺህ 445ኛ ዓመተ ሂጅራ የዒድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል። ሕዝበ ሙስሊሙ የዓረፋ በዓልን ሲያከብር በመተሳሰብ፣ በመረዳዳት እና በመደጋገፍ ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየወባ በሽታ ስርጭት የጤና ስጋት እየኾነ በመምጣቱ ከፍተኛ መሪዎች አጀንዳ አድርገው ሊሠሩ እንደሚገባ ተመላከተ።
Next article“የሀገር ችግር የሚፈታው በትምህርት በመኾኑ በሕጻናት ደረጃ ፆታን መሰረት አድርጎ የሚመጣ ማኅበራዊ ቀውስን መፍታት ያስፈልጋል” አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)