በሸዋሮቢት የተሃድሶ ስልጠና ማዕከል 287 ግለሰቦች የተሃድሶ ስልጠናቸውን አጠናቀው ተመረቁ፡፡

13

ባሕር ዳር: ሰኔ 07/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድፓስት በሸዋሮቢት ለአምስተኛ ዙር 287 የተሃድሶ ሰልጣኞች ለተከታታይ ስምንት ቀናት የተሃድሶ ስልጠና ወስደው ተመርቀዋል።

የተሃድሶ ሰልጣኞቹ በሰላም ምንነት፣ በሰላም አስፈላጊነት፣ ከግጭት እና ከጦርነት አዙሪት መውጫ መንገዶች፣ የጦርነት እና የግጭት ፈተናዎችን መሻገርያ መንገዶች እና ከሰልጣኞች የሚጠበቁ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በቂ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል።

ከማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድፓስት የተሃድሶ ስልጠና ማስተባበሪያ እንደ ተገኘው መረጃ በቀጣይም ወደ ማኅበረሰቡ ሲቀላቀሉ ከዚህ በፊት የነበረውን ጥፋታቸውን በማረም፣ ከአካባቢው ሕዝብ እና መንግሥት ጋር የሠላም አምባሳደር ኾነው እንደሚሠሩም በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ መግባባት ተፈጥሯል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ መንገድ ሥራዎች ድርጅት የዘመናት የመንገድ ጥያቄን መፍታት የቻለ ድርጅት መኾኑን በስልጤ ዞን የአሊቾ ውሪሮ ወረዳ ነዋሪዎች ገለጹ።
Next articleበደሴ ከተማ የትምህርት ተቋማት ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ኾኑ፡፡