በሰሜን ጎጃም ዞን ጎንጂ ቆለላ ወረዳ የተሠማራው የምሥራቅ ዕዝ ክፍለጦር 17 የፅንፈኛውን ቡድን አባላት በመደምሰስ፣ 12 በማቁሰል የጦር መሳሪያ መማረኩን ገልጿል።

118

የክፍለጦሩ አዛዥ ኮሎኔል አለም ታደለ አንድ ሬጅመንት በሰሜን ጎጃም ጎንጂ ቆለላ ወረዳ ብራቃትና ዴንሳ ባታ ቀበሌ ሕዝቡን በዘረፋ ሲያሰቃዩ በነበሩ የፅንፈኛው አባላት ላይ በወሰደው እርምጃ 12 ክላሽ 04 ሽጉጥ 08 የቃታ መሳሪያ 02 ጀኔነተር 03 ሞተር ሳይክልና 10 ጀሪካን ቤንዝን እንዲሁም የተለያዩ የመሳሪያ መጠገኛ ስፔር ፓርቶችን ማርከዋል ብለዋል።

ኮሎኔል አለም እንደተናገሩት የክፍለ ጦሩ ሬጅመንት በሰሜን ጎጃም ዞን ጎንጂ ቆለላ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ግዳጁን በመፈጸም የፅንፈኛውን ቡድን መንጥሮ እርምጃዎችን ወስዷል። በዚህም አንፃራዊ ሰላም ማስፈን መቻሉን ነው የገለጹት።

የአማራ ሕዝብ ሰላምን ሙሉ ለሙሉ ለማረጋገጥ ሰራዊታችን ቀንና ሌሊት ያለ እረፍት በቁርጠኝነት እየሠራ ይገኛል። የሰላሙ ባለቤት ኅብረተሰቡ በመሆኑ ከፌዴራልና ከክልል የፀጥታ ኀይሎች ጎን በመሆን የተለመደ አጋርነቱን አጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።

መረጃው የጎጃም ኮማንድ ፖስት ነው

Previous article“የ2017 ዓ.ም የፌደራል መንግስት በጀት የሕዝብን የልማት ፍላጎት መመለስ በሚያስችል መልኩ የተደለደለ ነው” አቶ አህመድ ሽዴ
Next article“በአካባቢያችን ያለው ሰላም ክልል አቀፍ ፈተናችንን በአግባቡ እንድንፈተን አግዞናል” በሰቆጣ ከተማ የ8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች