የሚኒስትሮች ምክር ቤት የበጀት ዓመቱን የመጨረሻ 100 ቀናት ግምገማ ጀመረ።

7

ባሕር ዳር: ሰኔ 04/2016 ዓ.ም (አሚኮ)የሚኒስትሮች ምክር ቤት የበጀት ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት የመጨረሻ የኾነውን የ100 ቀናት ግምገማ ዛሬ ጠዋት ጀምሯል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት ዛሬ ጠዋት የዘንድሮው የበጀት ዓመት ከመጠናቀቁ በፊት የመጨረሻ የኾነውን የሚኒስትሮች ምክር ቤት የመቶ ቀናት ግምገማ ጀምረናል ብለዋል። እንደሁልጊዜው የየሴክተሮችን አፈፃፀም እንገመግማለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ክፍተቶችን እናጤናለን፤ በጥንካሬዎች ላይ ለቀጣይ ሥራዎች እንነሳለን ብለዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በሚቀጥሉት ቀናት የሚጠበቀው እርጥበት በበልግ ዘግይተው ለተዘሩ ሰብሎች ጠቀሜታ ይኖረዋል” የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
Next article“ሁሉም ወረዳዎች የ8ኛ ክፍል ፈተናን እየሰጡ ናቸው” የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር