በሰሜን ወሎ ዞን የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች በሕወሓት እየተፈጸመ ያለውን ግፍ በሕዝባዊ ሰልፍ ገለጹ።

28

ባሕር ዳር: ሰኔ 02/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በሰሜን ወሎ ዞን የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች በሕወሓት በራያ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ግፍ በሕዝባዊ ሰልፍ ገልጸዋል።

ኢ- ሰብዓዊ ድርጊት በግፍ እየተፈጸመበት ያለው የራያ ሕዝብ ቁጣውን በአደባባይ ዛሬ ሰኔ 02/2016 ዓ.ም በሰሜን ወሎ ዞን አላማጣ ከተማ እየገለፀ ይገኛል።

ሕዝቡ የተለያዩ መፈክሮች በመያዝ እየደረሰበት ያለውን በማንነት ላይ የተመሰረተ ጭቆና አውግዟል።

👉ዛሬም ከአሸባሪነት ያልተለየው ወራሪውና አሸባሪው ትህነግ ሕጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ ኾኖ እንዲመዘገብ የሚደረገውን ሂደት አጥብቀን እንቃወማለን

👉የራያ ሕዝብ የማንነት ጥያቄ በሀገር አፍራሾች አይቀለበስም

👉እኛ ራያዎች አማራዎች ነን

👉የፌደራል መንግሥት ለራያ ሕዝብ አስቸኳይ ምላሽ ይስጥ

👉የፌደራል መንግሥት ሕግ ያስከብርልን

👉 የፕሪቶሪያው ስምምነት በአስቸኳይ እንዲፈጸም እንጠይቃለን ብለዋል።

ተጨማሪ መረጃ በቀጣይ ተከታትለን የምናደርስ ይኾናል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በጸጥታ ችግር ውስጥ ኾኖ ኘሮጀክቶችን በእቅድ መፈጸም የፓርቲውን የመፈጸም አቅም የሚያሳይ ነው” መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር.)
Next article“በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙት የልማት ሥራዎች ሀገሪቱ ወደ ብልጽግና ለምታደርገው ጉዞ ጉልበት ናቸው” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ