ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ በመዲናዋ የተገነቡ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ።

35

ባሕር ዳር: ሰኔ 01/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ እና የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ.ር) በአዲስ አበባ የተገነቡ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸውም የለሚ ኩራ የግብርና ምርት መሸጫ ማእከል፣ የእንስሳት ልማት እና ልህቀት ማእከል፣ ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ማበልጸጊያ ማእከል እንዲሁም ሌሎች የልማት ሥራዎችን ተመልክተዋል፡፡

በአዲስ አበባ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች እና ታላላቅ ፕሮጀክቶች የኅብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡና ለሌሎች ክልሎችም ተሞክሮ መኾናቸውን ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ተናግረዋል፡፡

በተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተገነቡት የልማት ሥራዎች ዝቅተኛ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉና የኑሮ ውድነቱን የሚያቃልሉ እንደኾኑ መግለጻቸውን ከከንቲባ ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበብልጽግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይ የፍቅርና የልማት ከተማ በሆነችው ጅማ ከተማ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።
Next article“ጥበባት መጪውን ትውልድ ቅርጽ በማስያዝ እና የከተማችንን የቱሪዝም መስሕብ በማላቅ ከፍ ያለ ሚና ይጫወታሉ” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)