
ባሕር ዳር: ግንቦት 30/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋገሾ እና የብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር እርስቱ ይርዳው የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ጎንደር ከተማ ገብተዋል። መሪዎቹ ጎንደር ከተማ ሲገቡ የአማራ ክልል መሪዎች፣ የከተማው ከንቲባ ባዩህ አቡሀይ እና ሌሎች የከተማው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ከጎንደር ከተማ ኮምዩኒኬሽን መምሪያ እንዳገኘነው መረጃ መሪዎቹ በጎንደር ከተማ ቆይታቸው በከተማዋ ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ይጎበኛሉ። ከተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር በሚደረጉ ውይይቶች ላይም ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!