ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከሳዑዲ አረቢያ ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ተወካዮች ልዑክ ጋር ተወያዩ።

42

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 29/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ከእስያ ጉብኝታቸው ማምሻውን በመመለስ የሶስት ቀናት የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን ካጠናቀቁት የሳዑዲ አረቢያ ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ተወካዮች ልዑክ ጋር ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱ በቤቶች ልማት በቱሪዝም እና በግብርና በተለይም በሀገር ውስጥ የማዳበሪይ ምርት ላይ ያተኮረ ነበር።

ሰባ ዘጠኝ ኢንቨስተሮችን ያካተተው ከፍተኛ ልዑክ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ.ር) እና የሳዑዲ አልጋ ወራሽ መሃመድ ቢን ሰልማን በሕዳር ወር በሳዑዲ – አፍሪካ ጉባኤ ወቅት ያደረጉትን የሁለትዮሽ ውይይት ተከትሎ የተከናወነ ነው።

መረጃው የጠ/ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ነው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ ሕዝብ ሙዚየም ታሪክ በወጉ የሚቀመጥበት እና የጎብኝዎች ማዕከል እንዲኾን ታስቦ እየተሠራ ነው።
Next articleበክልሉ እየተገነቡ የሚገኙ የኤሌክተሪክ ኃይል ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ልዩ ክትትል እየተደረገ ነው።