በመከላከያ ሠራዊት ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ የተመራ ልዑክ ጅቡቲ ገባ።

87

ባሕር ዳር: ግንቦት 29/2016 ዓ.ም (አሚኮ)በመከላከያ ሠራዊት ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ የተመራ ልዑክ በጂቡቲ የመከላከያ ሠራዊትን 47ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ለመታደም ጂቡቲ ገብቷል።

ክብረ-በዓሉ ላይ የጂቡቲ የመከላከያ ሚኒስትር ሀሰን ኦመር መሐመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የመከላከያ ሠራዊት አታሼዎች እና ዲፕሎማቶች በተገኙበት በተለያዩ ወታደራዊ ትርዒቶች መከበሩን ከጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ የማኀበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በ2016 በጀት ዓመት 10 ወራት ከዕቅዱ በላይ ኃይል አመንጭቶል።
Next articleበአማራ ክልል ከ8 ሚሊዮን በላይ የማኅበረሰብ ክፍሎችን በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማሳተፍ ዝግጅት እየተደረገ መኾኑ ተገለጸ።