ሰላምን ለማጽናት ታሳቢ ያደረገ ሕዝባዊ ውይይት በኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር እየተካሄደ ነው።

16

ባሕር ዳር፡ ግንቦት 24/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር “ውስጣዊ አንድነት ለዘላቂ ሰላም እና አብሮነት” በሚል መሪ መልዕክት በከሚሴ ከተማ ሕዝባዊ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። በውይይት መድረኩ የክልል፣ የብሔረሰብ አሥተዳደሩ፣ የወረዳ መሪዎች፤ አባ ገዳዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ነጋዴዎች፣ ምሁራን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የአማራ ክልል ብልጽግና ፖርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባጋራው መረጃ በጋራ ጉዳዮች ላይ ምክክር እያደረጉ እንደሚገኙ ገልጿል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleጦርነትን ኖረንበታል። የተወሰኑ ችግሮቻችንን ፈትተንበታል።
Next article“የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶችን ማጠናከር የሁሉም ኀላፊነት ሊኾን ይገባል” አሕመዲን መሐመድ (ዶ.ር.)