ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ካንፓኒዎች ጋር ተወያዩ።

19

ባሕር ዳር: ግንቦት 21/2016 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ እና በስሩ ከሚተዳደሩ ካምፓኒዎች ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሰፈሩት በካምፓኒዎች መፈፀም ስላለባቸው የኦዲት፣ የትርፍ ድርሻ ክፍያ እና ከሆልዲንጉ ጋር ባለው የሥራ ግንኙነት ሥለነበሩ መልካም አፈፃፀሞች መወያየታቸውን አመላክተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ፈጥነን በጋራ መፍታት እና መሻገር ስለሚገቡን ተግዳሮቶች ምክክር አድርገን ተግባብተናል” ሲሉም ገልጸዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleአምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከኒውዝላንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ።
Next article“ቤተ ክርስቲያን ፈተናን መሻገር የሚያስችል ተቋም መፍጠር ይኖርባታል” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ